• UoG Home
  • Home
  • About Us
    • About the School
    • Dean’s Message
    • Facility and Services
    • School Administration
    • Contact
  • Programs
    • LL.M
    • LL.B
  • School
    • School of law Programs
    • Staff Profile
    • Students
  • Research
    • Research
    • Technology Transfer
    • Community Services
    • The International Journal Of Ethiopian Legal Studies
  • (+251) 58 114 12 32
  • info@uog.edu.et
  • TV
  • Radio
  • Staff Profile
  • Event
  • Mail
School of Law
  • UoG Home
  • Home
  • About Us
    • About the School
    • Dean’s Message
    • Facility and Services
    • School Administration
    • Contact
  • Programs
    • LL.M
    • LL.B
  • School
    • School of law Programs
    • Staff Profile
    • Students
  • Research
    • Research
    • Technology Transfer
    • Community Services
    • The International Journal Of Ethiopian Legal Studies

Events

  • Home
  • Events
  • ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮችን፣ ተመላሾችን እና ጾታዊ ጥቃት ሰለባ የሆኑ ወገኖችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት ዛሬ አስጀምረናል።

ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮችን፣ ተመላሾችን እና ጾታዊ ጥቃት ሰለባ የሆኑ ወገኖችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት ዛሬ አስጀምረናል።

ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮችን፣ ተመላሾችን እና ጾታዊ ጥቃት ሰለባ የሆኑ ወገኖችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት ዛሬ አስጀምረናል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሚታወቅባቸዉ የማህበረሰብ አገልግሎቶች መካከል በህግ ት/ቤት በኩል የሚሰጠዉ የነጻ ህግ ድጋፍ መስጫ ማዕከል አገልግሎት አንደኛዉ ነዉ፡፡ ማዕከሉ በአንድ መልኩ ሌጋል ክሊኒክ ሆኖ የትምህርት ጥራትን ያስጠብቃል፤ በሌላ መልኩ ድምጽ ለሌላቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች ድምጽ በመሆን የማሕበረሰብ አገልግሎት መስጠት ነው።
ማዕከሉ በዋነኛነት አገልግሎት የሚሰጠው በሀገራችን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች እንዲሁም የመብት ጥሰቶች ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይ ሴቶች፣ ህፃናት፣ ሕሙማን፣ አካል ጉዳተኞች፣ አረጋዉያን እና በአጠቃላይ በገንዘብ እጥረት ምክንያት ጠበቃ መግዛት የማይችሉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን መብት የሚያስጠብቅ በመሆኑ የአገልግሎቱን ዋጋ የላቀ ያደርገዋል፡፡
ማዕከሉ በ2002 ዓ.ም ሲቋቋም አገልግሎቱን የጀመረው ጎንደር ከተማ በከፈታቸው 2 ማዕከላት ሲሆን በሂደት የማዕከላቱን ቁጥር 16 በማድረስ ወደ ብዙ ወረዳዎች በመቅረብ ተደራሽ ያልነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን መድረስ ተችሏል፡፡
በእነዚህ ማዕከላት አማካኝነት እስካሁን ከ40ሺ በላይ የሚሆኑ ተጠቃሚወችን ወክሎ ፍርድ ቤት መከራከርን ጨምሮ የተለያዩ የህግ ድጋፍ አገልግሎቶችን በነጻ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
በ”USAID የፍትህ ተግባራት በኢትዮጵያ” ድጋፍ ዛሬ በይፋ የተመረቁት የአዘዞ እና ደባርቅ ከተሞች ነጻ የሕግ ድጋፍ መስጫ ማዕከላትም የዚሁ አካል ናቸው፡፡
“USAID የፍትህ ተግባራት በኢትዮጵያ” ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ያደረገልን ሲሆን በቀጣይ አንድ ዓመት ገደማ የፕሮጀክት ቆይታ ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮች፣ ተመላሾች እና ጾታዊ ጥቃት ሰለባ የሆኑ ከ3000 በላይ ወገኖችን ተጠቃሚ ይሆናሉ።
በገጠመን የህልውና ጦርነት ምክንያት በርካታ ወገኖቻችን የተለያዩ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የስነ ልቡና ቀውሶች የተዳረጉ በመሆኑ የእነዚህ ማዕከላት መቋቋም ፋይዳው የጎላ ነው።
የገንዘብ ድጋፍ ላደረገልን “USAID የፍትህ ተግባራት በኢትዮጵያ”፣ ፍርድ ቤቶች፣ አቃብያነ ህግ ጽ/ቤቶች፣ የፖሊስ ጽ/ቤቶች፣ ማረሚያ ቤቶች፣ ፕሮጀክት ቀርጸው ይህን ፈንድ ላመጡና ነጻ የሕግ ማዕከላችን ላለፉት 12 ዓመታት ሳይቆራረጥ ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ በመሆን ሙያዊ ግዴታቸውን ለተወጡና እየተወጡ ላሉ የህግ ት/ቤታችን መምህራንና ተማሪዎችና ባለ ድርሻ አካላት ሊመሰገኑ ይገባል።

Start Time

8:00 am

February 20, 2022

Finish Time

5:00 pm

September 30, 2024

Address

maraki, Gondar

  • Share:

Leave A Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

  • Public and International Relations
  • +251 581 14 1232
  • info@uog.edu.et
  • Maraki Street, Gondar, Ethiopia
  • 196

Important Links

  • Registrar
  • Library
  • Ethics Application(REAMS)
  • Student Services

Resources

  • Student Information System (Internal)
  • Research and Ethics Application System (REAMS)
  • UoG Journals
  • Student Application System
  • Student Registration System
  • Student Placement System (Internal)
  • Research, TT and Community Service Portal

Copyright © 2022 University of Gondar | All Rights Reserved.